ዋሽንግተን ዲ.ሲ. – የሸማቾች የፋይናንስ ጥበቃ ቢሮ (CFPB) በወረርሽኙ የተጎዱ ተከራዮች እና አከራዮች የኪራይ፣ የመሠረታዊ አገልግሎቶች እና የሌሎች ወጪዎች የክፍያ እርዳታ በቀላሉ እንዲፈልጉ እና እንዲያመለክቱ የሚያስችል የኢንተርኔት መሣሪያ ዛሬ ይፋ አድርጓል። በ www.consumerfinance.gov/renthelp የሚገኘው "የኪራይ እርዳታ ፈላጊ"፣ በወረርሽኙ ወቅት ተከራዮች ከመኖሪያቸው ሳይፈናቀሉ እንዲቆዩ ለመርዳት በሀገር አቀፍ ደረጃ በቢሊዮኖች የሚቆጠር ዶላር የፌዴራል እርዳታ ከሚያሰራጩ የክልል እና የአካባቢ ፕሮግራሞች ጋር ተከራዮችን እና አከራዮችን ያገናኛል።

“በወረርሽኙ ምክንያት በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎች የቤት ኪራይ ዕዳ ወድቆባቸዋል፣ እንዲሁም ከቤት የመፈናቀል አደጋ ተጋርጦባቸዋል” ብለዋል የCFPB ጊዜያዊ ዳይሬክተር ዴቭ ኡኤጂዮ። “የኪራይ እርዳታ ፈላጊው፣ ተከራዮች እና አከራዮች በአካባቢያቸው የሚገኘውን የፋይናንስ እርዳታ በቀላሉ እንዲያገኙ ያደርጋል። በሀገሪቱ ውስጥ ያሉ ሰዎች ቀደም ሲል በቢሊዮኖች የሚቆጠር ዶላር እርዳታ በማግኘት ላይ ናቸው፤ በዚህ አዲስ መሣሪያ አማካኝነት ደግሞ ይበልጥ ቁጥራቸው በርከት ያሉ ተከራዮች እና አከራዮች ከዚህ የአደጋ ጊዜ እርዳታ ተጠቃሚ ይሆናሉ ብለን ተስፋ እናደርጋለን። ይህ ገንዘብ ለአከራዮችም ሆነ ለተከራዮች አሸናፊ የሚያደርግ ሲሆን፣ ወጪ ከሚጠይቁ እና አላስፈላጊ ከሆኑ መፈናቀሎች ይልቅ ለሁሉም የተሻለ ውጤት ነው።”

CFPB በዌበክስ (Webex) በኩል የኪራይ እርዳታ ፈላጊ መሣሪያውን የማሳያ ፕሮግራም ያካሂዳል። ዝርዝር መረጃው ከዚህ በታች ቀርቧል፡- ቀን፦ ረቡዕ፣ ጁላይ 28፣ 2021

  • ሰዓት፦ ከጠዋቱ 11:00 EDT
  • ሊንክ፦
  • የመግቢያ ኮድ፦ 199 090 4698
  • የይለፍ ቃል፦ zYJNnEbh@784 (እባክዎን የይለፍ ቃሉን ኮፒ አድርገው አይለጥፉት) ከጁን 23 እስከ ጁላይ 5 ከተደረገው የCFPB ትንተና መሠረት፣ በተከራይ አቤቶች ውስጥ የሚኖሩ 16 በመቶ የሚሆኑ አዋቂዎች በአሁኑ ጊዜ የኪራይ ክፍያ እንደዘገየባቸው ተናግረዋል። የኪራይ ክፍያ በዘገየባቸው አቤቶች ውስጥ ከሚኖሩት አዋቂዎች መካከል 49 በመቶ ያህሉ ወይም በግምት 3.6 ሚሊዮን የሚሆኑት በሚቀጥሉት ሁለት ወራት ውስጥ የመለቀቅ ዕድላቸው በከፊል ወይም በጣም ከፍተኛ እንደሆነ ይናገራሉ። ታይቶ የማይታወቅ የኢኮኖሚ ማገገሚያ ጥረት አካል በመሆን፣ የፌዴራል መንግሥት ኪራይ፣ የአገልግሎት ክፍያዎችን እና ሌሎች የመኖሪያ ቤት ወጪዎችን መክፈል ለማይችሉ አቤቶች ድጋፍ ለማድረግ ከ$46 billion በላይ መድቧል። ሁሉም 50 ግዛቶች እና በመቶዎች የሚቆጠሩ የአካባቢ፣ የጎሳ እና ሌሎች ፕሮግራሞች ገንዘብ በማከፋፈል ላይ ናቸው። የCFPB የኪራይ እርዳታ ፈላጊ መሣሪያ ተከራዮች እና አከራዮች በአካባቢያቸው ከሚገኙ የኪራይ እርዳታ ፕሮግራሞች ጋር እንዲገናኙ እና ያሉትን የገንዘብ ድጋፎች ለማግኘት የመጀመሪያዎቹን እርምጃዎች እንዲወስዱ ያመቻችላቸዋል። CFPB የመኖሪያ ቤት ባለቤቶች እና ተከራዮች መብቶቻቸውን እና ጥበቃዎቻቸውን ለመረዳት የሚያስችሉ መረጃዎችን ጨምሮ የሚያስፈልጓቸውን ግብአቶች ለማቅረብ በመላው የፌዴራል መንግሥት ከሚገኙ አጋሮች ጋር በጥብቅ እየሰራ ይገኛል። ከዩ.ኤስ. ጋር በመሆንየሸማቾች የፋይናንስ ጥበቃ ቢሮ ከግብርና፣ ከቤትና ከተማ ልማት፣ ከገንዘብ፣ ከቀድሞ ወታደሮች ጉዳይ ሚኒስቴሮች እና ከፌዴራል የቤት ፋይናንስ ኤጀንሲ ጋር በመሆን፣ ስለ እርዳታ አማራጮች፣ ጥበቃዎች እና ዋና ዋና የጊዜ ገደቦች የዘመኑ ወቅታዊ መረጃዎችን የሚሰጥ የፌዴራል መንግሥት ሁሉን አቀፍ እና ዋነኛ የመረጃ ምንጭ ሆኖ የሚያገለግለውን consumerfinance.gov/housing ድረ-ገጽ አዘጋጅቷል።

CFPB በኮቪድ-19 ወቅት ተከራዮችን ለመደገፍ ሌሎች እርምጃዎችን ወስዷል፤ ይህም በወቅቱ ከነበሩት የኤፍቲሲ (FTC) ጊዜያዊ ሊቀመንበር ሬቤካ ኬሊ ስሎተር ጋር በመሆን ህገ-ወጥ ከቤት የማስለቀቅ እንቅስቃሴዎችን ለመከታተል ቃል የሚገባ የጋራ መግለጫን፣ በወረርሽኙ ወቅት ከቤት ማስለቀቅ ጋር ተያይዘው ያሉ ህገ-ወጥ የዕዳ አሰባሰብ አሰራሮችን የሚዘረዝር ጊዜያዊ የመጨረሻ ደንብን፣ እና በወረርሽኙ ወቅት ከኪራይ እና ከቤት ማስለቀቅ መረጃ ሪፖርት ጋር የተያያዙ የፍትሐዊ የብድር ሪፖርት ሕግ ግዴታዎችን (በተለይም የኪራይ እርዳታ ክፍያዎች አያያዝን ጨምሮ) የሚያብራራ ማስታወቂያን ያካትታል።

የሸማቾች የፋይናንስ ጥበቃ ቢሮ የፌዴራል የሸማቾች ፋይናንስ ሕግን የሚተገብርና የሚያስፈጽም፣ እንዲሁም የሸማቾች የፋይናንስ ምርቶች ገበያዎች ፍትሐዊ፣ ግልጽ እና ተወዳዳሪ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የ21ኛው ክፍለ ዘመን ኤጀንሲ ነው። ለበለጠ መረጃ www.consumerfinance.gov ን ይጎብኙ።